አዳዲስ ዜናዎች

የቅርብ ጊዜ ልጥፍ


  •     | የወላይታ ዞን ዜና

  •     | የወላይታ ዞን ዜና

  •     | የወላይታ ዞን ዜና

  •     | የወላይታ ዞን ዜና

  •     | የወላይታ ዞን ዜና

የወላይታ ዞን ዜና



  • የህግ ታራሚዎች ጤንነታቸው የተጠበቀና አምራች ዜጎች እንዲሆኑ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ ስፖርት ለሁሉም በሁሉም ሥፍራ በሚል መሪ ቃል የወላይታ ሶዶ ማረሚያ ተቋም የህግ ታራሚዎች በጋራ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አካሄዱ። የ2016 ዓ.ም የወላይታ ሶዶ ማረሚያ ተቋም የህግ ታራሚዎች ልዩ ልዩ ስፖርታዊ ውድድር ተካሂዷል። የወላይታ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ደረጀ የስፖርት ውድድሩን በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ያስጀመሩ ሲሆን ታራሚዎች ጤንነታቸው የተጠበቀና አምራች ዜጎች እንዲሆኑ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ወሳኝ ነው ሲሉ ገልጸዋል። አቶ ወንድሙ አክለው ስፖርት አንድነትና እርስ በርስ ያለን ግንኙነት እንዲጠናከር የሚያደርግ እንደሆነ በማስረዳት የሥራ መፍጠሪያም ዘርፍ በመሆኑ የህግ ታራሚዎች ከዚህ ሲወጡ በተሰጥኦዋቸው በመሳተፍ የነገ ተወዳዳሪ ዜጎች ለመሆን በተዘጋጁ ስፖርታዊ ውድድሮች እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል አቶ ደለለኝ ደቻሳ በመምሪያው የስፖርት ዘርፍ ቡድን መሪ ሲሆኑ በስፖርት ፖሊሲው ማንኛውም ዜጋ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ መሥራት እንዳለበት በተቀመጠው መሠረት ለህግ ታራሚዎች ስፖርታዊ ውድድሮች መዘጋጀታቸውንና ስፖርት በመሥራት ጤናቸውን እንዲጠብቁ አንስተዋል። በቀጣይ ቀናትም የመረብና የጠረጴዛ ቴኒስ ውድድሮች እንዲሁም ከባህል ስፖርት የገበጣና ገመድ ጉተታ ውድድሮች የተዘጋጁ መሆናቸውን የገለፁት አቶ ደለለኝ የህግ ታራሚዎች በዞኑ በሚደረጉ ልዩ ልዩ የስፖርት ሻምፒዮናዎች በመሳተፍ ከተቋሙ በሚወጡበትም ጊዜ አምራችና ጤናማ ዜጎች እንዲሆኑ እንደሚያስችላቸው አብራርተዋል። በተቋሙ የስፖርት ዘርፍ ባለሙያ የሆኑት ኢንስፔክተር መስፍን ጀጎሌ በተቋሙ ያሉ ዜጎች ነገ ኅብረተሰቡን ሲቀላቀሉ ጤንነታቸው የተጠበቀ እንዲሆን ስፖርት አስፈላጊ መሆኑን በመግለጽ ላመቻቸው የዞኑ ስፖርት ምክር ቤት ምስጋና አቅርበዋል። ስፖርት ሰላም፣ ፍቅር አንድነት ነውያሉት ኢንስፔክተር መስፍን ነገ ለሀገር ልማት አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ወጣቶች እንዲወጡም ያስችላል ብለዋል። ስፖርት በጤና ላይ የሚመጡ በሽታዎችን እንደሚከላከልላቸው ያነሱት ታራሚዎች ታርመን ስንወጣም በልማቱ እንድንሳተፍ ያስችለናል ሲሉ ገልጸዋል። የስፖርት እንቅስቃሴ ከሱሰኝነት፣ ከስሜታዊነትና ከወንጀል ነፃ እንዲሆኑ እንደሚያደርግም ስፖርት ሲሠሩ የዞኑ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ያነጋገራው ታራሚዎች ገልጸዋል።

    October 15, 2023

  •     October 15, 2023

  •     October 13, 2023

  •     October 12, 2023

  •     October 11, 2023

  • ተጨማሪ ዜና...

ክልላዊ ዜና



  • የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ የዓለም ቅርስ ኮሚቴ የጌዴኦ ባህላዊ መልክዓ ምድር በዩኔስኮ በዓለም ቅርስነት እንዲመዘገብ ውሳኔ ማስተላለፉን በማስመልከት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ ርዕሰ መስተዳድሩ የዓለም ቅርስ ኮሚቴ የጌዴኦ ባህላዊ መልክዓ ምድር በዩኔስኮ በዓለም ቅርስነት እንዲመዘገብ ውሳኔ ማሳለፉን መሰረት አድርገው ባስተላለፉት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት የጌዴኦ ባህላዊ መልክዓ ምድር ቀልብን ከሚስቡ የቱሪዝም ኃብቶቻችን መካከል አንዱ ነው ብለዋል፡፡ የጌዴኦ ህዝብ ደን የሰው ልጅ ህይወት መሆኑን ቀድሞ የተረዳና እንደልጁ ተንከባክቦ ከትውልድ ትውልድ የሚያሸጋግር አኩሪ ባህል ያለው ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ባህላዊ መልክዓ ምድሩም የዚህ ድንቅ ባህል ውጤት ነው በማለትም አብራርተዋል። የክልሉ መንግስት የጌዴኦ ባህላዊ መልክዓ ምድር በዩኔስኮ በዓለም ቅርስነት እንዲመዘገብ ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ መቆየቱን የገለፁት ርዕሰ መስተዳድሩ የዛሬው ውጤት እንዲመዘገብ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የፌደራል መንግስት ተቋማት ምስጋና አቅርበዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በመግጫቸው የክልሉ መንግስት ከህዝቡ ጋር በመቀናጀት ለቅርሱ ዘላቂ እንክብካቤ በማድረግ፣ የቱሪዝም መስህብ እንዲሆን አበክሮ ይሰራልም በማለት በድጋሚ ለጌዴኦ፣ ለክልሉ ብሎም ለመላው የሃገራችን ህዝቦች እንኳን ደስ አለን ብለዋል።

    September 18, 2023

  •     August 31, 2023

  •     August 30, 2023

  •     August 11, 2023

  •     August 11, 2023

  • ተጨማሪ ዜና...

ሀገራዊ ዜና



  • የህዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን የጋራ ስብሰባ ዛሬ ይካሄዳል ወላይታ ሶዶ፤ መስከረም 28/2016፦ 6ኛው የህዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን የጋራ ስብሰባ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ይካሄዳል። በመክፈቻ ሥነ-ስርዓቱ ላይ ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፤ የ2016 ዓ.ም ዋና ዋና የመንግስት አቅጣጫዎችን የሚያመላክት ንግግር የሚያደርጉ ይሆናል። በንግግራቸው በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ፣ ዲፕሎማሲና ሌሎች ጉዳዮች ላይ የመንግስትን እቅድ ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል። በሁለቱም ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ መክፈቻ መርሃ ግብር የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጠሪዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይገኛሉ።

    October 9, 2023

  •     September 27, 2023

  •     September 22, 2023

  •     September 18, 2023

  •     September 18, 2023

  • ተጨማሪ ዜና...

ዓለም አቀፍ ዜና



  • " 20 ዓመት ፖሊስ ሆኜ ሰርቻለሁ። እስካሁን በሕይወቴ እንዲህ አይነት አሰቃቂ አደጋ አይቼ አላውቅም " - ኢንስፔክተር ሽመልስ ቦሬሳ ትላንት እሁድ ከአዲስ አበባ በስተሰሜን በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደጋም ወረዳ " ወርቢ " በምትባል ቦታ በደረሰ እጅግ አሰቃቂ የትራፊክ አደጋ የ13 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል። በአደጋው ሕይወታቸውን ካጡት 13ቱ ሰዎች መካከል መምህርት አስመሬ ጎሶማ እና አራት ልጆቿ ይገኙበታል። መምህርቷ የ18፣ 15፣ 8 እና የ1 ዓመት ልጆቻቸውን ይዘው ከአዲስ አበባ ወደ ጎሃ ጽዮን ቤተሰብ ጥየቃ እየጓዙ የነበረ ሲሆን፣ በአደጋው የእናት እና #የሁሉም_ልጆቻቸው ሕይወት አልፏል። ለዚህ የትራፊክ አደጋ ምክንያቱ ቁልቁለት ቦታ ላይ ከባድ የጭነት መኪና በሕዝብ ማመላለሽ ሚኒባስ ላይ ስለወጣበት መሆኑን በደገም ወረዳ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት አሳውቋል። የፖሊስ ጽ/ቤት ኢንስፔክተር ሽመልስ ቦሬሳ ምን አሉ ? ኢንስፔክተር ሽመልስ ቦሬሳ ፦ " አደጋውን ያደረሰው የጭነት ተሽከርካሪ ከአዲስ አበባ ወደ ባሕር ዳር 500 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ተሳቢ መኪና ነው። ቁልቁለት ላይ ጥንቃቄ በጎደለው ሁኔታ ሲጓዝ ነበር። ከባድ ተሸከርካሪው ቁልቁለት መንገድ ላይ ከቁጥጥር ውጭ ከሆነ በኋላ ሁለት መኪኖችን ገጭቶ በመጨረሻ የሕዝብ ማመላለሻ ሚኒባስ መኪና ላይ ሙሉ በሙሉ ስለወጣበት በውጡ የነበሩ ሰዎችን ለሞት ዳርጓል። የ13ቱ ሰዎች ወዲያውኑ ነው ሕይወታቸው ያለፈው፤ ሌሎች ሦስት ሰዎች ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸው በኩዩ ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገላቸው ነው። አደጋው የደረሰባቸው ሰዎች ሲጓዙበት የነበረው ሚኒባስ ሙሉ በሙሉ ወድሟል ፤ ሌሎች ሦስት ተሸከርካሪዎች ላይም ከባድ ጉዳት አጋጥሟል። 20 ዓመት ፖሊስ ሆኜ ሰርቻለሁ። እስካሁን በሕይወቴ እንዲህ አይነት አሰቃቂ አደጋ አይቼ አላውቅም። የሰዎችን አስክሬን ማውጣት በራሱ እጅግ ሰቅጣጭ ነበር። በሕዝብ ማመላለሻ ሚኒባሱ ውስጥ ከነበሩት መካከል በሕይወት የወጡት ሁለት ብቻ ናቸው ፤ እነርሱም ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል። የአካባቢው መንገድ ጠመዝማዛማና ቁልቁለታማ ከመሆኑም በላይ ወቅቱ የዝናብ በመሆኑ አሸከርካሪዎች በከፍተኛ ጥንቃቄ ማሽከርከር አለባቸው። "

    July 17, 2023

  •     December 13, 2022

  •     December 2, 2022

  •     November 28, 2022

  •     November 23, 2022

  • ተጨማሪ ዜና...

ስፖርት



  • የጌዴኦ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል ዳራሮ 'ዳራሮ' 5 ኪሜ ሩጫ በዲላ ከተማ ተካሂዷል። በሩጫው የከተማው ነዋሪዎች፣ የጤና ስፖርት ቡድን አባላትና በአካባቢው የሚሰለጥኑ ታዳጊ አትሌቶች ተሳትፈዋል። በወድድሩ ከወንዶች ሳሙኤል ገናሌ፣ አለማየሁ አለሙ እና ዘላለም አማዶ ከአንደኛ እስከ ሦሥተኛ ድረስ ያለውን ደረጃ ይዘው ያጠናቀቁ ሲሆን ከሴቶች አዛለች አለማየሁ፣ ለምለም ደሳለኝ እና መድኃኒት ዘሩ ከአንደኛ እስከ ሦሥተኛ ድረስ ያለውን ደረጃ ይዘው አጠናቅቀዋል። ለአሸናፊዎቹ የሜዳሊያና ገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

    January 28, 2023

  •     January 18, 2023

  •     January 10, 2023

  •     January 10, 2023

  •     December 26, 2022

  • ተጨማሪ ዜና...

ቢዝነስ



  • የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ከወንጀል ተግባር ጋር ግንኙነት ያላቸውን ከ600 በላይ የባንክ ሂሳቦች ማገዱን አስታወቀ። አገልግሎቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ ከወንጀል ተግባር ጋር ግንኙነት ያላቸው የባንክ ሂሳቦችን እንዳገደ አስታውቋል። ከህገ-ወጥ የውጭ አገራት ገንዘብ ማስተላፍ ወንጀሎች ጋር ግንኙነት እንዳላቸው የተጠረጠሩ 665 የባንክ ሂሳቦች እንዳይንቀሳቀሱ ማገዱን ነው የገለጸው። በአገልግሎቱ የታገዱት የባንክ ሂሳቦቹ ህጋዊ የውጭ አገራት ገንዘብ ማስተላለፍ ፈቃድ ሳይኖራቸው በህገ-ወጥ መንገድ በአገር ውስጥ እና በውጭ አገራት ከሉ አካላት ጋር ትስስር በመፍጠር በህገ-ወጥ መንገድ የገንዘብ ማስተላለፍ ተግባር ላይ ተሰማርተው የተገኙ መሆናቸው ታውቋል። በወንጀል ድርጊቶቹ ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ተሳትፎ የነበራቸውን አካላት በህግ ተጠያቂ የማድረግ የተጠናከረ ሥራ በመከናወን ላይ ይገኛል ብሏል። የተለያዩ የወንጀል ድርጊቶችን በመፈፀም የተገኘን ሃብት ከህጋዊ ምንጭና በህጋዊ መንገድ የተገኘ በማስመሰል የመጠቀም ወንጀሎች አፈፃፀም በየጊዜው እየተቀያየረ ያለ ወንጀል ከመሆኑም ባሻገር ከወንጀል ድርጊቶቹ የተገኘው ሃብት ሽብርተኝነትን በገንዘብ በመርዳት ወንጀል መፈፀሚያ ጭምር የሚውል በመሆኑ የመከላከልና መቆጣጠር ስራው በተጠናከረ አግባብ በመከናወን ላይ ይገኛል። ስለሆነም የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎቱ ከባላድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት እነዚህን ወንጀሎች ለመከላከልና ለመቆጣጠር በሚያደርገው ሂደት ህብረተሰቡ መረጃና ጥቆማ በመስጠት የተለመደ ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል።

    October 10, 2022

  •     August 16, 2021

  •     August 16, 2021

  •     August 16, 2021

  •     August 16, 2021

  • ተጨማሪ ዜና...

| የአየር ሁኔታ


WOLAITA SODO WEATHER

| የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች


ሳይንስና ቴክኖሎጂ



  • አፍሪካ ባላት እምቅ የተፈጥሮ ሀብት ልክ እንድታድግ የአፍሪካውያን የእርስ በእርስ ግንኙነት የበለጠ ማደግ እንዳለበት ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ገለጹ።

    በአዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው 6ኛው የአፍሪካ ኢንጂነሪንግ ጉባኤ መክፈቻ ላይ ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ እንዳሉት የመሰረተ ልማት ፍላጎትና አቅርቦት በፍጥነት እያደገ ነው።

    አፍሪካ መልማትና መበልጸግ የሚያስችላት የተፈጥሮ ሀብት ቢኖራትም ተባብሮ መስራት አለመቻል ትልቅ ፈተና ሆኖ ቆይቷል ብለዋል።

    አህጉሪቱ ያላትን እምቅ አቅም መጠቀም ትችል ዘንድ በአፍሪካውያን መካከል የእርስ በእርስ ግንኙነቱ ከዚህ በላይ ማደግ እንዳለበት ገልጸዋል። የአፍሪካ ኢንጂነሮች ጉባኤ አፍሪካን በመሰረተ ልማት ለማስተሳሰር ጉልህ ድርሻ እንዳለው የገለጹት ፕሬዝዳንቷ፤ይህ አይነቱ ምክክር ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።

    ኢትዮጵያ የሸገርና አንድነት ፓርክ ፕሮጀክቶችን በመገንባት አፍሪካውያን ኢንጂነሮች አፍሪካን መቀየር እንደሚችሉ አሳይታለች ብለዋል።

    ጉባኤው በኢንጂነሮች መካከል ጤናማ የውድድር መንፈስ በመፍጠር የአፍሪካን የመሰረተ ልማት ግንባታ ፈጣንና ጥራት ያለው እንዲሆን ያግዛል ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ዮናስ አያሌው ናቸው።

    November 8, 2022


  •     August 16, 2021

  •     August 16, 2021

  •     August 16, 2021

  •     August 16, 2021

  • ተጨማሪ ዜና...

ጤና



  • የኢየሩሳሌም ከፍተኛ የህክምና ቡድን በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ ነፃ የህክምና አገልገሎት ለመስጠት ካራት ከተማ ገቡ።

    የህክምና ቡድኑ ለተከታታይ አምስት ቀናት የሚቆዩ ሲሆን ከ10 ሺህ በላይ ህሙማንን ለማከም ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

    የጄዊሽ ቮይስ ኢንተርናሽናል የህክምና ቡድን ኮንሶ ማህበረሰብን በነፃ የህክምና አገልግሎት ለማገልገል ካራት ከተማ ሲደርሱ የኮንሶ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ ገልገሎ ገልሾ፣ ካራት ከተማ ከንቲባ አቶ ፍሬዘር ኮርባይዶ እና ከፍተኛ የዞንና ከተማ አመራር እና የህክምና ባለሙያዎች ደማቅ አቀባበል አድርጎላቸዋል።

    ነፃ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ካራት ከተማ የገቡት እንግዶቹ ከ18 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የመዲሃኒት፣ የህክምና ቁሳቁስ፣ የምርመራ ማሽኖች፣ የምርመራ ግብዓትና ሌሎች ቁሳቁስን አሟልተው መግባታቸው ታውቋል።

    ማንኛውም የጤና ችግር ምርመራና የማዳን ስራ ለማድረግና ህብረተሰቡን በነፃ ለማገልገል የገባው የህክምና ቡድን በካራት ከተማ በተደረገላቸው አቀባበል ተደስተው በሚኖራቸው ቆይታ ሁሉ አገልግሎቱን በብቃት ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን በደስታ አስታውቀዋል።

    ነፃ የህክምና አገልግሎቱ ከነገ ህዳር 25 ጀምሮ ለተከታታይ አምስት ቀናት እንደሚሰጥ ይጠበቃል።

    መረጃው የኮንሶ ዞን መንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉ/መምሪያ

    December 3, 2022


  •     November 23, 2022

  •     November 17, 2022

  •     November 5, 2022

  •     August 16, 2021

  • ተጨማሪ ዜና...

አለም በፎቶግራፍ